ባህሊዊ የእስሌምና ትምህርት መገለጫዎች፣ለውጦችና ወቅታዊ ተጨባጮች በወሎ ቃሉና ቦረና አካባቢዎች

Authors

  • አሚናት አብደ ዐመር አማርኛ ትምህርት ክፍል፣ ወል ዩኒቨርሲቲ፣ ደሴ-ኢትዮጵያ

DOI:

https://doi.org/10.20372/ajcik.2022.1.1.693

Abstract

ጥናቱ የተካሄደው ‹‹ባህሊዊ የእስሌምና ትምህርት መገለጫዎች፣ለውጦችና ወቅታዊ ተጨባጮች በወሎ ቃሉና ቦረና አካባቢዎች›› በሚሌ ርዕስ ሲሆን የባህሊዊ ትምህርቱን መገለጫዎች በማብራራት ለውጦችንና ወቅታዊ ተጨባጩን መተንተን የጥናቱ ዋና አላማ ነው፡፡ ጥናቱ አይነታዊ ምርምርን ተከትሎ ተካሂሌ፡፡ በመሆኑም ቃለ መጠይቅ ምልከታና የተተኳሪ ቡድን ውይይትን በመረጃ መሰብሰቢያነት፣ ገሊጭ የመረጃ መተንተኛ ዘዴን ደግሞ በመረጃ መተንተኛነት ተጠቅሟል፡፡ የጥናቱ ውጤት እንደሚያመለክተው ባህሊዊው የእስሌምና ትምህርት እንደማስተማሪያ ዘዴነት ሸሪካ፣ ሙጠላ፣ መዋጣት፣ መከረር(መሀፈዝ)፣ መሰማትና ውርድ የተባሉ ልማዶችን ይጠቀማል፡፡ ተማሪዎች ደረሳ የሚባሉ ሲሆን በአዳሪነትና በተመላላሽነት ትምህርታቸውን ይከታተላሉ፡፡ ትምህርቱ ቁርአንና ኪታብ ተብል የሚከፈል ሲሆን በቁርአን ጁዝ የሚባሌ ክፍሌፋይ አለው፡፡ በዚህም የተማሪው የትምህርት ደረጃ ይገለጻል፡፡ በኪታብ ዯግሞ በሚማረው ኪታብ ስም ዯረጃው ይታወቃሌ፡፡ ይህ የትምህርት ዯረጃ በሙስሉሙ ማህበረሰብ ውስጥ ቋሚ የሆነ እውቀትን መነሻ ያዯረገ መዋቅር እንዴፇጠር አስችሎሌ፡፡ በመሆኑም ባህሊዊው የእስሌምና ትምህርት የህብረተሰብን ታህታይ መዋቅር ሇማስጠበቅ አስተዋጽኦ እንዲሇው ጥናቱ አረጋግጧሌ፡፡ ባህሊዊው የእስሌምና ትምህርት ገጠርን ማዕከሌ ያዯረገ፣ ጠንካራ ተቋማዊ መሰረት ያሇው፣ ሀገር በቀሌ ስርዓተ ትምህርትን በወጥነት የሚጠቀም፣ በአብዛኛው ሇፉቅህና ሇቋንቋ ትምህርቶች ትኩረት የሚሰጥ መሆኑ መገሇጫዎቹ ናቸው፡፡ ከዚህ አንጻር አሁን ባሇው ተጨባጭ በባህሊዊ ትምህርቱ ሊይ ሇውጦች እንዯተከሰቱም በጥናቱ ተረጋግጧሌ፡፡ በመሆኑም ባህሊዊ ትምህርቱ ከገጠር ወዯ ከተማ በመዘዋወር ሊይ እንዯሆነ ፣ከጠንካራ ተቋማዊነት ይሌቅ ትስስር በላሇው የተቋሞች አዯረጃጀት አሌፎ አሌፎም በግሇሰባዊነት ዯረጃ በመሰጠት ሊይ እንዯሚገኝ፣ ወጥ የሆነ ስርዓተ ትምህርትን እየተከተሇ እንዲሌሆነ፣ ከይዘት አንጻር ዯግሞ ከፉቅህ ሇሀዴስና ሇተፍሲር ትምህርቶች ትኩረት ሰጥቶ እንዯሚያስተምር ጥናቱ አረጋግጧሌ፡፡ እነዚህ ሇውጦች ዯግሞ በሙስሉሙ ማህበረተሰብ መካከሌ ተመሳሳይ ሏይማኖታዊ ግንዛቤ እንዲይኖር፣ ሰፉው የገጠሩ ሕብረተሰብ ትምህርቱንና ጭብጡን አዱስ ብል በጥርጣሬ እንዱያየው፣ እንዱሁም በህብረተሰቡ መካከሌ የነበረው እውቀትን መሰረት ያዯረገ መዋቅር እንዱፊሇስና ግሇሰቦች ሃይማኖታዊ ዯረጃቸው እንዲይታወቅ ብልም የማእረግ ስሞች በተገቢው ሁኔታ ጥቅም ሊይ እንዲይውለ አዴርጓሌ፡፡

Keywords:

ባህሊዊ, የእስሌምና ትምህርት, ለውጥና ተጨባጭ

Downloads

Published

2022-12-27

How to Cite

ዐመር አ. አ. . (2022). ባህሊዊ የእስሌምና ትምህርት መገለጫዎች፣ለውጦችና ወቅታዊ ተጨባጮች በወሎ ቃሉና ቦረና አካባቢዎች. Abyssinia Journal of Culture and Indigenous Knowledge, 1(1), 27–40. https://doi.org/10.20372/ajcik.2022.1.1.693

Issue

Section

Articles